Login
Main menu

ታሪከ አበው: ​ኢያሱ

Download
Name
Play
Size
Duration
download
ኢያሱ ከፍል 3
Yeneta

52.5 MB
1:08:06 min
download
ኢያሱ ከፍል 2
My Recording

101.7 MB
1:14:04 min
download
ኢያሱ ከፍል 4
yeneta

120.2 MB
1:27:30 min
download
ኢያሱ ከፍል 1
yenta

32.6 MB
41:38 min

Read more...

ፍና ቅዱሳን

መጽሐፉን ለማግኝት 

+251 923976850

+251 911249756

ከመጽሐፉ የተወሰደ 

 

‹‹የእግዚአብሔርን ቃል የተናገሩአችሁን ዋኖቻችሁን አስቡ፤ የኑሮአቸውን ፍሬ እየተመለከታችሁ በእምነታቸው ምሰሉአቸው ፡፡ ዕብ. 13÷7

The paradise ወይም The Garden of the Fathers በሚለው ታላቅ መጽሐፍ፤ የእስክንድርያው ቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊ ፤ የሄሊያ ፓሊስ ሊቀ ጳጳስ ጳላድዮስና ቅዱስ ጄሮም፤ ዘመናቸው ታላቅ የቅድስና ሕይወትን በመምራት ይታወቁ የነበሩ አበውን በአካል በማግኘትና፤ በአካል ለማግኘት ያልቻሉትንም ከደቀ መዛሙርቶቻቸው በመጠየቅ የተጋድሎ ሕይወታቸውንና ድንቅ የሆኑ ምክሮቻቸውን መዝግበው ትተውልናል፡፡ 

በአባቶች ዘንድ የቅድስናን ሕይወት ለመኖር የነበረን ቁርጠኝነት፤ ለወጣንያን የሥጋ ፈቃድን መቆጣጠርና የቅድስናን ሕይወት መለማመድን የሚያሳዩበት መንገድ ጌታ መንፈስ ቅዱስ ለቃኘው ኅሊና እጅግ መሳጭ ነው፡፡ ሰውነቱን ለእግዚአብሔር ሕያውና ቅዱስ መስዋዕት አድርጎ ለማቅረብ ለሚመኝ ሁሉ የቅዱሳንን ሕይወት ከማንበብ የሚበልጥ ነገር አይገኝም፡፡

የንስሐቸው ጥልቀት ልብን ይሰብራል፤ የተጋድሏቸው ትዕግሥት ከዓለት ይልቅ ይጸናል፤ ምክርና ተግሣፃቸው የልብን ሸለፈት ለመግረዝ  ከባልጩት ይልቅ ይሰላል፤ ለጌታ እግዚአብሔርና ለሰው ልጅ ያላቸው ፍቅር ዕንባን በዓይን ይሞላል፤ ትኅትናቸው በትዕቢት ያበጠ ኅሊናን ያፈርሳል፤ ጸሎታቸው እንደ በረሃ የደረቀ ሰውነትን ያረሰርሳል፡፡ እምነታቸው ሕሙማነ ሥጋ ወነፍስን ለመፈወስ፤ የዲያብሎስንም ወጥመድ ለመበጣጠስ በልዑሉ ፊት ብርቱ ነው፡፡ ለእኛ የሕይወት መምህራን የክርስትናም አብነቶች ናቸው ቅዱሳን፡፡ 

ቤተክርስቲያን የቅዱሳንን ታሪክ የምትዘግበው ታሪክ የማስተማር ዓላማ ኖሯት አይደለም፡፡ ያ ቢሆን ኖሮ በቤተክርስቲያን ያልተመዘገቡ የስንቶች ታሪክ ታልፎ አይቀርም ነበር፡፡ ዋና ዓላማዋ ከቅዱሳን ሕይወት እንድንማርና የእነርሱን የተጋድሎ ጥበብ እንድንወርስ ነው፡፡

የዚህ መጽሐፍ ዓላማውም፡-

ሀ. በወንጌል በቃል (theory) ደረጃ ተቀምጦ የምናየውን ክርስትና እንዴት በተግባር መተርጎም (practical) እንደሚቻል ለማመላከት

ለ. የክርስትና ሕግ ከዚህ ዓለም ጠባይና ከሰው ድካም አንጻር ሊፈፀም የማይችል ሕግ ነው ብሎ ለሚያስብ፤ ጌታ እግዚአብሔር ሊፈፀም የማይችል ሕግ እንዳልሰጠንና፤ በሚደንቅ ጽናት የክርስትናን ሕይወት ኖረው ያለፉትን በማየት ከመንፈስ ዝለት ለመራቅ፤

ሐ. መጽሐፍ ቅዱስንም ሆነ ሌሎች ቅዱሳት መጻሕፍትን ለምናነብ ሁሉ እንዲሁ በልማድ፤ ለእውቀት፣ የቋንቋ ክህሎትን ለማዳበር ወዘተ... ሳይሆን በእያንዳንዷ ነጥብ ራሳችንን በመመርመርና ከሕይወታችን ጋር በማገናኘት መሆን እንዳለበት ለማስገንዘብ ታስቦ የቀረበ ነው፡፡

ይህን መጽሐፍም ሆነ ሌሎችን ተመሳሳይ መጻሕፍትን የሚያነብ ሁሉ ዓላማውን መሳት የለበትም፡፡ ባወቅነው መጠን መጠየቅ አለና በተረዳነው ለመኖር መጋደል ይጠበቅብናል፡፡ በወንጌል የተገለጠው ክርስትና በተግባር ተፈጽሞ የምናየው በቅዱሳን ሕይወት ነው፡፡

ክርስትና የሕያው እግዚአብሔርን ልጅ ክርስቶስ ኢየሱስን መምሰል ነው፡፡ የቅዱሳን ምክር ደግሞ እኛ እርሱን እንደመሰልን እኛን ምሰሉ፤ በዕለት ተዕለት ኑሯችሁም እግዚአብሔርን ለመምሰል ራሳችሁን አስለምዱ የሚል ነው፡፡ ይህን ቋሚ የኑሮ መርሕ በማድረግ በየጊዜው የሚታይ ለውጥ ማሳየት ከክርስቲያን የሚጠበቅ ነው፡፡ ብዙዎቻችን መለወጥን አብዝተን እንፈልጋለን፡፡ የዘወትር ጥያቄያችንም እንዴት መለወጥ እችላለሁ? የሚል ነው፡፡ እውነታው ደግሞ የዚያኑ ያህል ለውጥን፤ ጠባዬ የምንለውን አሸንፈን በወንጌል አዲስ ሰው መሆንን አጥብቀን እንፈራለን፡፡ ለውጥ እንዲሁ አይመጣም፡፡ ለመለወጥ ማመን፣ መሻት፣ መወሰን ከዚያም ተጋድሎ ያስፈልጋል፡፡ በቅዱሳኑ ሕይወት የምናየውም ይኸው ነው፡፡ 1ጢሞ. 4÷ 8 ፤ 1ቆሮ 11÷1

የቅዱሳንን ታሪክና የኑሮ ፍሬ ከያዘው <<The Paradise>> ወይም <<The Garden of the Fathers>> መጽሐፍ ላይ የተወሰዱ የተወሰኑ ታሪኮች በዚህ መጽሐፍ ተካተዋል፡፡ ከእያንዳንዱ ታሪክ ለጥቆም ለሁሉም ሊመጥን በሚችል ደረጃ የተወሰኑ ማብራሪያዎች ቀርበውበታል፡፡ በታሪኮቹና በማብራሪያው ውስጥ፡- እውነተኛ ንስሐ ከተለምዶ የከንፈር ኑዛዜ ምን ያህል እንደሚለይ፤ የተሻለውን ስለ መምረጥ፣ ውሳኔ በክርስትና ውስጥ ምን ያህል ሥፍራ እንዳለው፣ በትንሹ ለምናማርርም በመከራ መታገስ ምን እንደሚመስል፣ ምክር መስማትና ተግሳፅን መቀበል ሕይወትን እንዴት እንደሚለውጥ፣ ራስን ለሌሎች አሳልፎ መስጠትና በክርስቶስ የሆነ ፍቅር የማይቻለውን እንዴት እንደሚያስችል፤ የይቅርታን ታላቅ ኃይልና በትዕቢትም የሚገጥመንን ውድቀት ለመዳሰስ ተሞክሯል፡፡ በእያንዳንዱ ታሪክ ላይ የቀረበውን መንፈሳዊ ልምምድም በአቅማችን ግን በጽናትና በታማኝነት ለመለማመድ እንድንጥርም ተጋብዘናል፡፡

የእውነተኛ መንፈሳዊ መጻሕፍት ምንጭ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ነውና፤ መጽሐፉን ያዘጋጀሁት ከሚያነቡት ከብዙዎች ራሴን እንደ አንዱ አድርጌ ነው፡፡ የሁላችን መምህር እርሱ ነው፤ ሁላችን ደግሞ ደቀ መዛሙርት!

መጽሐፉን ስናነብ ቢያንስ አንድ ለሕይወታችን የሚጠቅም ነገር እንድናገኝ አምላከ ቅዱሳን ይርዳን!

መልካም ንባብ !

ቀሲስ ታምራት ውቤ

ነሐሴ 2008 ዓ.ም

 

Read more...

ጠቃሚ አድራሻዎች

መጻሕፍት ቢያነቧቸው

  • * ​ፍቅር 
  • ፍና ቅዱሳን
  • * የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ሕይወቱ እና ትምህርቱ 
  • * ዝጎራ