Login
Main menu

በዚች ዓመት ደግሞ ተዋት

Index

 

እንኪያስ ፍሬ እንዲገኝብን ምን እናድርግ?

፩.ሁልጊዜ የጌታ እግዘአብሔርን ቃል በማስተዋል በማንበብ ሕይወታችንን ማሳደግ ‹‹ነገር ግን በእግዚአብሔር ሕግ ደስይለዋል ሕጉንም በቀንና በሌሊት ያስባል እርሱም በውኃ ፈሳሾች ዳር እንደተተከለች ፍሬዋን በየጊዜዋ እንደምትሰጥ ቅጠልዋም እንደማይረግፍ ዛፍ ይሆናል››መዝ ፩÷፪-፫

፪.ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ፍጹም ሕብረት ያለው ሕይወት ለመምራት መጣር ይህም የቃሉን ትምህርትና የሕይወቱን አብነት በማየትና እርሱን ለመምሰል ራስን በማስለመድ የሚገኝ ነው፡፡ ጌታችን ሲመክረን‹‹ እውነተኛ የወይን ግንድ አኔ ነኝ ገበሬውም አባቴ ነው ፍሬ የማያፈራውን በእኔ ያለውን ቅርንጫፍ ሁሉ ያሰወግደዋል ፍሬ የሚያፈራውንም ሁሉ አብዝቶ እንዲያፈራ ይጠራዋል… ‹‹ በእኔ ኑሩ እኔም በእናንተ፡፡ ቅርንጫፍ በወይኑ ግንድ ባይኖር ከራሱ ፍሬ ሊያፈራ እንዳይቻለው እንዲሁ እናንተ ደግሞ በእኔ ባትኖሩ አትችሉም፡፡ እኔ የወይን ግንድ ነኝ እናነተም ቅርንጫፎች ናችሁ ያለ እኔ ምንም ልታደርጉ አትችሉምና በእኔ የሚኖር እኔም በእርሱ ብዙ ፍሬ ያፈራል፡፡ በእኔ የማይኖር ቢሆን እንደ ቅርንጫፍ ወደ ውጭ ይጣላል ይደርቅማል፡ እነርሱንም ሰብሰበው ወደ እሳት ይጥሏቸዋል ያቃጥሉአቸውማል፡፡›› ክርስቲያን ተብሎ የክርስቶስ ኢየሱስ ቃሉንና ሕይወቱን የማይከተል ቢኖር የተገነጠለ የደረቀ ወደ እሳትም ለመጣል የተዘጋጀ ቅርንጫፍ ነው፡፡ ዩሐ ፩፭÷፩-፭ችሁጫፎችውምሸለቆችትናንን፣ፍርድኩሰትን

፫.ጸሎት፡- በሥርዓተ ቅዳሴ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱስ ሥጋውና ክብር ደሙ ለዘላለም ሕይወት ሲታደል በዜማ በሚጸለየው ጸሎት ላይ ‹‹ ሀበኒ እግበር ፍሬ ዘያሠምረከ›› እንላለን፡፡ አንተን ደስ የሚያሰኝ ፍሬ ሃይማኖት እሠራ ዘንድ ኃይል መንፈሳዊ ስጠኝ በማለት በሥጋው እና በደሙ እንማጸናለን፡፡ ይህም የተወደደና የተጋባ ጸሎት ነው፡፡

ዮሐንስ መጥምቅ ለአይሁድ‹‹ እናንተ የእፉኝት ልጆች ከሚመጣውቁጣ እንድትሸሹ ማን አመላከታችሁ; አንግዲህ ለንስሓ የሚገባ ፍሬ አድርጉ…›› በማለት ከገሠጸ በኋላ አብርሃም አባትአለን የሚሉት ከንቱ ትምክህት አብርሃማዊ ሃይማኖትና የመንፈሳዊ ፍሬ ካልተገኘባቸው ሥልጣነ እግዚአብሔር ከአብረሃም ልጅነት ቆርጦ እንደሚጥላቸው አስጠንቅቋቸዋል፡፡ በእኛ እንዲሁ ነው፡፡ በስሙ ክርስቲያን ተብለናል ከእመቤታችን በጸጋ ተወልደናል የቅዱሳን ቤተሰብሆነናል ካልን በእነርሱ የታየ ሕይወት ሊታይብን ግድ ነው፡፡ ካለበዚያ አንቆረጣለን፡፡

.የበለሷ ጌታ የበለሷ ፍሬ አለማፍራት ብቻ ሳይሆን ያሳሰበው ያለ ፍሬ በመቆየቷ ምድሩን ጭምር እያጎሳቆለች በመሆኑም ነው፡፡በመጀመሪያው የክርስትና ዘመናት አህዛብ ወደ ክርስትና በእጅጉ ይስባቸው የነበረ የክርስቲያኖች ስብከት ብቻ ሳይሆን ይታይባቸው የነበረው ተወዳጅ ምግባር ነበር፡፡ ክርስቲያኖች በፍቅራቸው፣በትዕግስታቸው፣በትኅትናቸው፣በታማኝነታቸው፣ሀሰትን፣ዝሙትን፣ርኩሰትን፣ፍርድ ማጉደልን፣መማለጃ(ጉቦ)መቀበልን፣ዘፈንና፣ስካርን ጠብንና ክርክርን፣ተንኮልና አድመኝነትን፣ትዕቢትንና በሌሎች ላይ መፍረድን ወዘተ… በመጥላታቸው ይታወቁ ነበር፡፡ በሰላም ሆነ በመከራ ጊዜ በማግኘትም ሆነ በማጣት፣በሞትም ሆነ በሕይወትም ፍቅራቸው የማይቀዘቅዝ ደስታቸው የማይበረዝ ነበር፡፡ ስለዚህ ብዙዎችን በሕይወት በሚገለጥ ስብከት እስከ ሞት ለታመኑት አምላክ ማርከዋል፡፡ ዛሬ ግን እኛ ክርስቲያኖች እንደሚጠበቅብን ባለመሆናችን እንኳን ከውጭ ያሉት ተማርከው ሊገቡ ከውስጥ ያሉት እየወጡ ተቸግረናል፡፡

ፍሬ አለማፍራታችን ከራሳችን አልፎ ለሌሎችም የማሰናከያ ድንጋይ ስለሚሆን ነው‹‹ቁረጣት›› የሚል ትዕዛዝ ከልዑሉ የሚወጣው፡፡ የቅዱሳን ምልጃ የመላእክትና የካህናት ጸሎት ጌታ እግዚአብሔርን ከመዓት ወደ ምህረት ከቁጣ ወደ ትዕግሥት ባይመልሰው በዚህች ደቂቃ ይህን ጹሑፍ ለማንበብ እንኳ አንበቃም ነበር፡፡

ከእኛ ቀድመው የተጠሩ ፍሬ ተገኝቶባቸው ወይም ምድሪቱን በክፋት ሥራ አጎሳቁለው እንደተጠሩ የሚያውቅ ጠሪው ብቻ ነው፡፡ እኛ ለመፍረድ እውቀቱም ሥልጣኑም የለንም፡፡

እኛ ግን የቆየነው ከሁለቱ ባንዱ ምክንያት ነው፡፡ መንፈሳዊ ፍሬ ተገኝብቶናል አልያም ‹‹ቁረጣት›› ተብሎ የመላእክቱና የቅዱሳን ምልጃ ታድጎናል፡፡ ግን ስለ እኛ በዚህ ዓመት ደግሞ ተዋት ወደፊት ብታፈራ ደህና ነው ያለዚያ ግን ትቆርጣታለህ፡፡

ቅዱስ ጴጥሮስም ‹‹የአህዛብን ፈቃድ ያደረጋችሁበት በመዳራትና በሥጋም ምኞትም በስካርም በዘፈንም ያለ ልክም በመጠጣት ነውርም ባለበት በጣዖት ማምለክ የተመላለሳችሁበት ያለፈው ዘመን ይበቃል›› ሲል መስክሯል ባለፈው ዓመት ግብረ አህዛብን ለመፈጸም ለመዳራት፣ለስካር ለሥጋ ምኞት፣ለዘፈን፤ሀሰት ለመናገር ወዘተ… ጊዜ፣ገንዘብ፣ኃይል፣ ቁርጠኝነት፣ሕብረት ከነበረን ለሚያግደን ምክንያትም መንገድ እንዳልሰጠን ፈቃደ እግዚአብሔርን ለመፈጸም፣ራስን ለመግዛት፣በወይን ጠጅ ሳይሆን በመንፈስ ለመሞላት፤ለመንፈሳዊ ምኞት፣ለዝማሬ፣ እውነትን ለመመስከር፣ለሚሰድቡን ለመጸለይ በሌሎች ላለመፍረድ ወዘተ…ጊዜ፣ገንዘብ፣ኃይል፣ቁርጠኝነት፣ሕብረት፣ምክንያትን መሰበር በእኛ ዘንድ ሊገኝ የተገባ ነው፡፡ በዚህ ከመቆረጥ እንድናለን፤ለምንኖርባት ምድር መልካም አርአያ እንሆናለን ጊዜያችን ደርሶ ብንሄድም የሕይወትን ጽዋ እነቀበላለን ከቅዱሳን ሕብረትም እንደመራለን፡፡

 

ወስብሐት ለእግዚአብሔር

ቀሲስ ታምራት ውቤ

 

2006ዓ.ም.


Leave a comment

Make sure you enter the (*) required information where indicated. HTML code is not allowed.

back to top

ጠቃሚ አድራሻዎች

መጻሕፍት ቢያነቧቸው

  • * ​ፍቅር 
  • ፍና ቅዱሳን
  • * የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ሕይወቱ እና ትምህርቱ 
  • * ዝጎራ