Login
Main menu

ትውልዱ ከእመቤታችን ምን ይማራል?

Index

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን!

ትውልዱ ከእመቤታችን ምን ይማራል?

መግቢያ

‹‹ጐሥዐ ልብየ ቃለ ሠናየ›› በማለት አባ ሕርያቆስ በእመቤታችን ስም(ለእመቤታችን) በደረሰው ቁርባን ምስጋናው ስለ እመቤታችን ንጽሕናና ቅድስና፤ አካላዊቃልን በሥጋ  በመንፈስ ቅዱስ ግብር ለመውለድ መብቃት እንደቻለች፤ የአበው ተስፋ የነቢያትም ትንቢትና ምሳሌ በእርሱዋ እንዴት እንደተፈጸመ አምልቶ አስፍቶ ተናግሯል፡፡ ሊፈጽመውግን አልቻለም፡፡ ነቢዩ ዳዊት ‹‹ጐሥዐ ልብየ… ልቤ በጎ ነገርን አፈለቀ እኔ የንጉሥን ሥራ እናገራለሁ››፤ ብሎ ቅድመ ዓለም ያለ ፍጡራን አምላክ፣ ያለ ተገዢ ጌታ፣ ያለ ሎላልት ንጉሥ የሆነ፤ ድህረ ዓለም በማኅፀነ ማርያም በተዋህዶ ኋላም በመስቀል የነገሠ የእግዚአብሔርን ሥራ እናገራለሁ ብሎ ቢጀምር ሊፈጽመው እንዳልቻለ የአባ ሕርያቆስም እንዲሁ ነው፡፡መዝ 44፥1

ስለ ምሥጢረ ሥላሴ(ስለ እግዚአብሔር አንድነትና ልዩ ሦስትነት) በቅጥነተ ኅሊና ሊመረምሩ የወደዱ ብዙ ሊቃውንት፤ስለ አካላዊ ቃል በተለየ አካሉ ፍጹም ሰው መሆን የማይወሰነው መወሰኑ ርቀትን ከግዘፍ፣ኃይልን ከድካም፣ባዕልነትን ከንድየት፣ሕያውነትን ከመዋቲት ፍጹም በሆነ ተዋሕዶ ሳይቀላቀሉ ሳይለያዩ ሳይጠፋፉ አንድ ማድረግ፤ ጉምቱ ጉምቱ መንፈሳውያን ሊቃውንት ጠንቅቀው ሊጽፉ የሞከሩ ቢሆንም አንዳቸውም ግን ይህን ማድረግ ሳይቻላቸው ድካማቸው ስዒን በወለደው አንክሮ ተደምድሟል፡፡

የጌታ እግዚብሔር ባሕርይ የመድኃኒታችንንም ሰው የመሆን ምሥጢር ጠንቅቆ ፈፅሞ መናገር እንዳይቻል፤ የአብ ሙሽራ የወልድ ማደሪያ የመንፈስ ቅዱስ ንጽሕት አዳራሽ ስለሆነች ስለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም በእርሷ ስለተደረገ ነገርና ስለ ክብሯ ጠንቅቆ ፈጽሞ መናገር አይቻልም፡፡

‹‹ነኪር ነገሩ በእንቲአኪ ሀገረ እግዚአብሔር›› እንዳለ ነብዩ ዳዊት የእግዚአብሔር ከተማ ሆይ በአንቺ የተከበረ(ድንቅ) ነገር ይባላል ሲል ነው፡፡ቃሉ ቃለ አንክሮ ነው፡፡‹‹ድንቅ›› የሚለው ቃ አንክሮ ከአእምሮአችን በላይ ለሆነ የተከተተ መግለጫ ልንሰጠው ለማንችለው ጉዳይ የምንጠቀምበት ነው፡፡እመቤታችን ብሥራተ መልአኩን ከተቀበለች በኋላ ‹‹እስመ ገብረ ሊተ ኃይለ ዐቢያተ››አብ ቢሉ በልጁ ወልድ ቢሉ በሥልጣኑ ምድራዊ ባይደ ሰማያዊ፤ ተፈጥሯዊ ባይደለ አምላካዊ፤ ጊዜያዊ ያይደለ ዘላለማዊ ታላቅ ሥራን በእኔ አድርጓል ብላ መስክራለች፡፡መዝ 86፥3 ፤ሉቃ 1፥49

          እንዚራ መንፈስ ቅዱስ የተባለ ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ ስለ እመቤታችን በጻፈው ድርሰቱ በብዙ ሕብረ አምሳል እየመሰለ ሲያወድሳት ቢቆይም የእርሷን ክብርና ገናናነት ተናግሮ መፈጸም እንደማይቻል ከተረዳው በመንፈስ ቅዱስ የተቃኘ ሰውነቱ‹‹ኑ ዘይክል ነቢ ዕበየኪ ወአልቦ ዘይመስል ኪያኪ›› ትርጉም ‹‹ክብርሽን ተናግሮ መፈጸም የሚችል ማነው? አንቺን የሚመስልሽ የለምና››ሲል መልካም ነገርን አፍልቋል፡፡

          የምሥጋና አባቱ(መምህሩ)ነዩ ዳዊት ስለ ጌታ እግዚአብሔር‹‹መኑ ይመስለከ እም አማልክት እግዚኦ›› ‹‹አቤቱ ከአማልክት አንተን የሚመስልህ ማነው?›› ብሎ የልዑሉን ገናናነት እንደተናገረ፤ ከአማልክት የሚተካከለው ያይደለ የሚቀርበው፤የሚቀርበው ያይደለ የሚመስለው የሌለ የልዑሉ ዙፋን፤እርሱን በማኅፀኗ ተሸክማ በሥጋ ወልዳ ዓለማትን በረቂቅ በግዘ የሚመግበው ጡቶቿን አጥብታ ያሳደገች የእርሷም ክብር ገናንነት መናገር አይቻልም ሲል በምሥጢር መስሎታል፡፡ውዳሴ ማርያም ዘዓርብ

ጨምሮም ‹‹ዕበያ ለድንግል ኢይትከሀል ለተነግሮ እስመ እግዚእ ረያ›› የድንግል ክብሯ ጠንቅቆ ይነገር ዘንድ አይቻልም ጌታ መርጧታልና፡፡አብ ቢሉ ለልጁ ማደርያ እንድትሆን ወልድ ቢሉ ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ነሥቶ ከእርሷ ሰው ይሆን ዘንድ መርጧታልና፡ መምረጡንም ቅድመ ሥጋዌ ቢሉ በነቢያት ትንቢት፤ ጊዜ ጋዌ ሉ በመልክ ብራት፤ ድኅረ ሥጋዌ ቢሉ ሥጋን ነስቶ በመታየት፣ በሐዋርያት ትምህርት፣ በሊቃውንት መጻሕፍት አስረድቶናል፡፡ውዳሴ ማርያም ዘሠሉስ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤ/ክ ምዕመናን፤ እንዲሁም በእምነት በቀኖና የሚመስሏቸው ሌሎች የአኃት አብያተ ክርስቲያናት ምዕመናን ዳዊት በመዝሙሩ‹‹ወዘሕጎ ያነብብ መዐልተ ወሌሊተ ወይከውን ከመ ዕፅ እንተ ትክልት ኀበ ሙሐዘ ማይ፤እንተ ትብ ፍሬሃ በበጊዜሃ ወቈፅላኒ ኢይትነገፍ›› እንዳለ የነያትን ትንቢት፣የሐዋርያትን ትምህርት፣ የሊቃውንትን የትርጓሜ ድርሳናት፣ ከንፁሕ ምንጭ ስለ አምላካቸው ታላቅነት፤ ስለ እመቤታችንም ንፅሕና ቅስና ክ አማላጅነት ሲጠጡ በመኖራቸው ልምላሜ ነፍስ ሳይለያቸው ሥራ ሊሠሩ በተሰጣቸው ጊዜ የንስሐ ፍሬ የመንፈስ ፍሬ በማፍራት በትሩፋት ላይ ትሩፋት እየጨመሩ የእርሷን ጸጋ ክንፈ ረድዔት በማድረግ እንደ ንስር በመንፈሳዊ ሕይወትና እውቀት ሲመጥቁ ይታያሉ፡፡መዝ 1፥2-3

ክርስቲያን ለመባልና የልጅነትን ክብር ለማግኘት የቻልነው አካላዊ ቃል ከእመቤታን ተ  የቤዛነትን ሥራ በመፈጸም ዓለምን ካዳነ በኋላ ነው፡፡‹‹በስሙ ለሚያምኑ የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣን ሰጣቸው›› እንዲል፡፡ ወረደ ተወለደ መከራን ተቀበለ ተሰቀለ ሞተ ተነዐረገ ዳግመኛ በሕያዋንና በሙታን ለመፍረድ ይመጣል ብሎ ሥጋን ተዋሕዶ በፈፀመው ሥራና ስመ ሥጋዌውን ስመ ሥርየት ስመ ድኅነት ነው በማለት ማመን ነው፡፡ይህ ሁሉ የተፈፀመ ከእርሷ በነሳው ሥጋ ነው ብሎ የሚያም በነገረ ድኅነት ውስጥ ያለውን የእመቤታችንን ሱታፌ መገንዘብ አይሳነውም፡፡


Leave a comment

Make sure you enter the (*) required information where indicated. HTML code is not allowed.

back to top

ጠቃሚ አድራሻዎች

መጻሕፍት ቢያነቧቸው

  • * ​ፍቅር 
  • ፍና ቅዱሳን
  • * የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ሕይወቱ እና ትምህርቱ 
  • * ዝጎራ