Login
Main menu

ትውልዱ ከእመቤታችን ምን ይማራል?

Index

 

          በኦሪት ጽላት ያደረበት(የተቀመጠበት)ታቦት በሚታይ ገንዘብ የእስራኤል ዘሥጋ የአምልኮታቸው ማዕከል ነበር፡፡ እግዚአብሔርም ቃሉን የሚያሰማቸው በታቦቱ ላይ በመገለፅ ነበር፡፡ እስራኤል ታቦቱን ይዘው ባህር ተከፍሎላቸው ቅጥር ፈርሶላቸው ጠላት ጠፍቶላቸው ምደረ ስት ከነዓንን ወርሰዋል፡፡ታቦት የእመቤታችን ጽላት የጌታ ምሳሌ መሆኑ በብዙ መተርጉማን የተብራራ ነው፡፡ የአዲስ ኪዳን ቤተ ክርስቲያንም የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን አዳኝነትና የእመቤታችንን ምልጃ ማዕከል አድርጋ አምልኮዋን ትፈጽማለች፡፡ ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም የጌታችንን መወለድ በልባቸው ይዘው ያመኑ፤ በአፋቸውም የእርሱን አምላክነት የእርሷን ወላዲተ አምላክነት የሰከሩ ምዕመናን በጥምቀት በሚገኝ ልጅነት ጥቅመ ኃጢአት ፈርሶላቸው ዲያብሎስን ድል ነስተው ርስ መንግሥተ ሰማያትን ለመውረሳቸው ምሳሌ ነበር፡፡

ቅድስት ድንግል ወላዲተ አምላክ ማርያምን አልቦ (ያገለለ) ክርስትና የለም፡፡በዚህ የተቃኘ ትምህርትም ከአባቶቻችን ከሐዋርያትና ከሊቃውንት የተገኘም አይደለም፡፡ ወንጌላውያኑም እመቤታችን በወንጌል በነገረ ድኅነት የነበራትን ሱታፌ በግልጽ ጽፈውታል፤ከጽን እስከ በዓለ ጵራቅሊጦስ፡፡ ጌታችን ካረገ በኋላ እንኳ ሐዋርያት እርሷን  እንደ ታቦት በመካከላቸው አድርገው ይጸልዩ ነበረ ፡፡ጸሐፊው‹‹የኢየሱስም እናት በመካከላቸው ነበረች›› ብሎ የጻፈ ያለ ምክንያት አይደለም፡፡

ጌታችን ልጅነትን የምናገኝበትን ሥርዓ ጥምቀት አስቀድሞ በግብር ፈፅሞ ምሳሌ በመሆን ኋላ በቃ ከውኃና ከመንፈስቅዱስ ካልተወለዳችሁ ወደ እግዚአብሔር መንግስት ልትገቡ አይቻላችሁም እንዳለ፤ በመስቀሉ ላይ በዮሐንስ አማካኝነት በእርሱ ለሚያምኑ ሁሉ‹‹እነኋት እናትህ›› ‹‹እነሆ ልጅሽ›› ብሎ በቃሉ እናት አድርጎ ከመስጠቱ በፊት ከእርሷ በመወለዱ ልጆቿ አድርጎናል፡፡ ሊቃውንትም የእግዚአብሔር የባሕርይ ልጁ በመሆኑ እኛን በጸጋ የእግዚአብሔር ልጆች አደረገን ‹‹ወደ አባቴ ወደ አባታችሁ. . .›› እንዲል፤ ከድንግሊቱም ተወለዶ የድንግሊቱ ልጆች አደረገን ብለው አመስጥረውታል፡፡የዮሐንስ አፈወርቅ የማቴዎስ ወንጌል ትርጓሜ ማቴ1፥25-ፍጻሜ

ጌታ ቅድመ ዓለም አካል ዘእምአካል ባህርይ ዘእምባህርይ ከአብ እንደተወለደ፤ ድኅረ ዓለም ደግ ከእመቤታችን ፍጹም የሰውን ባህርይ በመያዝ በግዘፍ አካል ነስቶ ተወልዷል፡፡‹‹ንሕነ አባላቲሁ ለክርስቶስ››እ የክርስቶስ ብልቶቹ(አካሉ)ነን እንዲል ቅዱስ ጳውሎስ በምሥጢር የክርስቶስ አካሉ የምንባል ክርስቲያኖች ሁሉ ከእርሷ ተወልደናል፤ እናትነቷም ተሰጥቶናል፡፡ ‹‹እምነ ጽዮን ይብል ሰብእ ወብእሲ ተወልደ በውስቴታ›› ‹‹ሰው እናታችን ጽዮን ይላል ከእርሷ ሰው ተወልዷልና›› ዳለ ክቡር ዳዊት ከአዳም በሥጋ የተወለደ ሁሉ እንደሞተ፤ ከእርሱ(ከክርስቶስ) በመንፈስ የሚወለድ ሁሉ ለዘላለም በሕይወት እንዲኖር ከእርሷ ተወልዷልና ሰው እመቤታችንን ጸወነ ሥጋ ጸወነ ነፍስ(የነፍሳችንና የሥጋችን መጠጊያ መጽናኛ) እናታችን ሲላት ይኖራል ሲል የተናገረው ሁሉ በዚህ ተፈጽሟል፡፡1ቆሮ6፥15፤1ቆሮ12፥12-27፤መዝ86፥5

እመቤታችን በክርስትና ካላት ቦታ በትንሹ ይህ ካልን በልጇ አምን ክርስቲያን የተባልን ሁላችን ከእናትነቷ ምን ተምረናል? በወንጌል ከተገለጠው የእመቤታችን ሕይወት ምን ወስደናል? በእርግጥስ እንደ እናትነቷ እኛ የክርስትና ሕይወት ለእርሷ ደስታ የሚሆን ነው? የሚለውን ማንሳት ያስፈልገናል፡፡

ይህንን እንድናነሳ ያስገደደን በአብዛኛው ስለ እርሷ በማስተማር እንጂ ከእርሷ ፍጹም ልዩና የተቀደሰ ሕይወት ስንማር አንታይምና ነው፡፡ከእመቤታችን ሕይወት ልንወርስ የሚገቡንን  አርአያ ቅድስና (መልካም ነገሮች) መንፈስ ቅዱስ በዘመናት በሊቃውንት አንደበት በቅዱሳን ሕወት አድሮ እንዳስተማረን ሁሉ ከእርሱ የተቀበልነውን እንዲሁ እናቀብላለን፡፡

1ኛ. ትህትና፡- በእመቤታችን ሕይወት የምናየው በቃላት ከመገለጽ በላይ የሆነ ትኅትና ነው፡፡ ሊቃውንት ወትሮም እመቤታችን መጽሐፈ ኢሳያስን ስታነ‹‹እነሆ ድንግል ትጸንሳለች ወንድ ልጅም ትወልዳለች ስሙን አማኑኤል ብላ ትጠራዋለች›› ብሎ ከተናገረው ብትደርስ እኔ በሆንኩ አላለችምከዚች ድንግል ደርሼ ወጥቼ ወርጄ ባገለገልኳት አለች እንጂ፡፡ ኢሳ7፥14

ዛሬ ክብርን ሁሉ የከፍታ ወንበርን ሁሉ ለራሱ የሚመኝ እንጂ ለሀገር ለቤተክርስቲያን እንዲህ የሚራ ተነስቶ እኔ አገልጋዩ ሆኜ ባለፍኩ የሚል ማግኘት አስቸጋሪ በሆነበት ጊዜ ይህን የእመቤታችንን የትኅትና ሕይወት ማስተዋል ያስፈልገናል፡፡ተመርጠው ለክብር የሆኑትንም ስናይ ቀርቦ ማገልገል እንጂ መተቸት ለውጥ አያመጣም፡፡ ዛሬ ሁላችን የምንጨነቅ ሌላውን ስለመለወጥ እንጂ ስለራሳችን መለወጥ አይደለም፡፡

የእመቤታችን ትኅትና በመልአኩ ብስራትም ተገልጸ_ል፡፡ ያንቺ ጽንስ እንደ ሌሎች ሴቶች አይደለም ካንቺ የሚወለደው ቅዱሱ የእግዚአብሔር ልጅ ነው ባላት ሰዓት‹‹እነሆ የጌታ አገልጋ (ገረዱ)እንደ ቃልህ ይሁንልኝ›› በማለቷ ታውቋል፡፡ እናቱ ትሆኛለሽ ሲላት ለልጇ አገልጋዩ መሆንዋን በመግለጽ ነበር ትኅትናዋን ያሳየች፡፡

ጌታ በመስቀል ሳለ ለዮሐንስ ‹‹እነኋት እናትህ››ለእመቤታችንም ‹‹እነሆ ልጅሽ›› ብሎ ሲያረካክባቸው፤ ከጌታ ጋር ኖሬ አገልጋይ፣ ከመምህር ጋር ኖሬ ከደቀመዝሙር፤ ከፈጣሪ ጋር ኖሬ ከፍጡር  አላለችም ዮሐንስ ወደ ቤቱ ሲወስዳት በትኅትና ተቀለች እንጂ፡፡ ስንቶቻችን ይሆን ከታናናሾቻችን ጋር እነርሱን መስለን መኖር የምንችል? ከታላላቆች ጋርማ ማንነታችንን ሸጠን ክብራችንን ጥለን እምነታችንን ሰውተን አንገታችንን እንደከዘራ ቆልምመን መኖርን እናውቅበታለን፡፡ ለፍርፋሪ ስንል!!!


Leave a comment

Make sure you enter the (*) required information where indicated. HTML code is not allowed.

back to top

ጠቃሚ አድራሻዎች

መጻሕፍት ቢያነቧቸው

  • * ​ፍቅር 
  • ፍና ቅዱሳን
  • * የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ሕይወቱ እና ትምህርቱ 
  • * ዝጎራ