Login
Main menu

ትውልዱ ከእመቤታችን ምን ይማራል?

Index

 

7. በራዊ ሕይወት፡- እመብርሃን ቅድስት ድንግል ማርያም የኤልሳቤጥንመነስ ከመልአኩ እንደሰማች ፈጥና ነው ወደ ኤልሳቤጥ የሄደችው፡፡ ያቺ እግዚአብሔርን በመፍራት የምትኖር የካህን ሚስት ስለቷ ተሰምቶ በመልአክራት ወንድ ልጅ መነሷን ስትሰማ ደስታዋን ለመካፈል አልዘገየችም፡፡ በሰው ሀዘን ተደስቶ በባልንጀራው ደስታ የሚከፋ በበዛበት በዚህ ክፉ ዓለም የእርሷን አርአያ መከተል ምንኛ መቀደስ ነው፡፡ቅዱስ ጳውሎስም ‹‹ደስ ከሚላቸው ጋር ደስ ይበላችሁ፣ሚያዝኑ ጋር አልቅሱ››ያለ የሰውን ስሜት በቅንነት መካፈልክርስቲያናዊ ምግባር በመሆኑ ነው፡፡ሮሜ 12፥15፤ ሉቃ 1፥57-65

          ከእግዚአብሔር የሆነን ነገር ደግሞ የሰዎቹን ደስታ ከመካፈል ባለፈ ማድነቅ ይገባል፡፡ለኤልሳቤጥ ከእግዚአብሔር እንደሆነው ሁሉ ለሕዝቡ ጥቅም ከእግዚአብሔር የሆነ ስጦታ(ጸጋ) የተሰጣቸው ስንመለከት

ሀ. እግዚአብሔር በእርሱ አድሮ ስለሠራው ድንቅ ሥራ

ለ.እግዚአብሔር በእርሱ አድሮ ሕዝቡን ስለመጥቀሙ

ሐ.በዘመናችንም ዓይኖቻችን የእርሱን ድንቅ ሥራ በማየታቸው ልንደሰት ይገባናል፡፡ ከእግዚአብሔር በሆነ ጸጋ መቅናት፤ሰዎቹ ሩት ሥራ እንቅፋት መሆን ከእግዚአብሔር ጠላቶች ጋር መሰለፍ ነው፡፡

8. ድንግልና፡- የእመቤታችን ድንግልና፡-

ሀ. በሥጋ በኅሊና በመሆኑ( ድንግል በኅሊናኪ ወድንግል በሥጋኪ) እንዲል

ለ.ሕዋቶቿ በሙሉ የተጠበቁ መሆናቸው ማለት የኃጢአት መግያ ከሆኑት ከርዕይ ከሰሚዕ ከገሢሥ ከአንዎ የተጠበቀች መሆኗ( ከማየት፣ከመስማት፣ከመዳሰስ፣ከማሽተት)

ሐ.ቅድመ ጸኒስ ጊዜ ጸኒስ ድኅረ ጸኒስ ፤ቅድመ ወሊድ ጊዜ ወሊድ ድኅረ ወሊድ ድንግልናዋ ለቅጽበት ያልተለወጠ መሆኑ(ድንግልናዋ እናት በመሆኗ ያልተለወ መሆኑ)ልዩ ያደርጋታል፡፡ይህ ለሌሎች ሴቶች አይቻልምና‹‹ከሴቶች ተለይተሸ››ያሰኛት ቅሉ አንዱ ይህ ነው፡፡

          በተፈጥሮ ርዓት አንዲት ሴት ሙሽራዋን እስክታገኝ(እስኪመጣ)ራሷን በመግዛት እንደምትጠብቅ፤ ያ ካልሆነ ግን ከክብር እንደምታንስ በመንፈሳዊው ይወትም ነፍሳችንን በኃጢት ከክብር ከማነስ ጠብቀን ድንግልና የተባለ ልጅነታችንን በሃይማኖት በምግባርሙሽችን የሆነው ክርስቶስ እስኪመጣ እንጠብቃለን፡፡

ለእርሱ ለክርስቶ የሸለመች ሙሽራ ሆነን እንዴት ባለ የነፍስ ቅድስና መጠበቅ እንዳለብን የተሰጠችን ሕያው ምሳሌ ደግሞ እመቤታችን ነች፡፡ በእርሷ በአካል ያደረ በእኛ በጸጋ ያድርብናልና፡፡የዮሐ.ራዕ 21፥2

9.ጸሎት፡- እመቤታችን የመልአኩን ብሥራት የኤልሳቤጥንና የዮሐንስን ምሥክርነት ከተቀበለች በኋላ የተናገረችው ጸሎት ዘመናት በአላውያን ነገሥት በአረማውያን እንዲሁም በመናፍቃን የተነሣባትን የጥፋት ማዕበል ለመሻገር ለቤተክርስቲያን ጉልበት የሆነ ነው፡፡ጸሎቷም ምን ያህል በቅዱሳት መጽሐፍት እውቀት የበለጸገ የልዑሉንም ሥራ በማስተዋል የከበረ መሆኑ ተገልጦ የሚታይ ነው፡፡  ፍጹም በነፍሷ ለእግዚአብሔር ያላትን ክብር፣ ትኁታኑን ማይረሳ መሆኑን፤ ቅድስናውን፣ እውነተኛ ፈራጅ መሆኑን፣ለሚፈሩት የሰጣቸውን ቃል ኪዳን የማይረሳና ምህረቱም ለልጅ ልጅ መሆኑን የገለጠ ነው፡፡በከንፈ እግዚአብሔርን የሚያከብሩና በነፍሳቸው ልዑሉን የሚፈሩ የጸሎታቸው ልዩነት ለማነጻጸር ከሚቻል በላይ ነው፡፡ ጸሎተ ማርያም ዛሬም ድረስ በቤተክርስቲያን ለካህናት ሞገስ ለሕሙማን ፈውስ፤ ለሀገር ሰላም ለርኁባን ምግብ፤ለመምህራን ጽናት ለደቀመዛሙርት እውቀት የሆናቸው ለዚህ ነው፡፡ሐዋርያትም በጸሎታቸው ወቅት እርሷን ይዘው መጸለያቸው የጸሎታቸው ምላሽ ይፈጥን ዘንድ ነው፡፡የእርሷ ጸሎት ተሰሚ ጉዳይ ፈጻሚ መሆኑን በቃና ርግ በግልፅ ማት ይቻላል፡፡ ‹‹የወይን ጠጅ እኮ የላቸውም››ብላ ለልጇ ከነገረችው በኋላ ድጋሚ መጠየቅ አላስፈለጋትም ‹‹የሚላችሁን አድርጉ›› አለች እንጂ፡፡ ደራሲ‹‹አልቦ ጸሎት ወአልቦ ትንባሌ እንሌኪ ድንግል ዘየዐርግ ሉዐሌ››ያለ ይህን ማስተዋል በመቻሉ ነው፡፡በመሆኑም እመቤታችንን ሳትይዝ ጸሎት ልመና አቀርባለሁ የምትል ቤተክስቲያን ብትኖር እርሷ ሐዋርያት የሰበሰቧት ቤተክርስቲያን አለመሆኗ በዚህ ይታወቃል፡፡

0. ምስጋና፡- እመቤታችን በእርሷ ላይ ይሆን ዘንድ ልዑሉ የፈቀደው ከሆነ በኋላ ይን የተረዱ እነ ኤልሳቤጥ ተፀውዖ ስሟ ማርያም ብለው መጥራታቸውን እንደማይገባ ድፍረት አድርገውስለቆጠሩት፤ የእርሷም ከቤታቸው ጣሪያ በታች መግባት የተገባቸው እንዳልሆነ ስለተረዱት‹‹የጌታዬ እናት ወደ እኔ ትመጣ ዘንድ እንዴት ይሆንልኛል?››በማለት ክብሯን ገልጠው መሰከሩ፡፡እቤታችን ጌታን ፀንሳ ከወለደች በኋላ በወንጌል እንዲሁ ‹‹ማርያም›› ተብላ ስትጠራ አናገኝም፡፡ወንጌላውያኑ ሁሉ ‹‹የሕጻኑ እናት›› ‹‹የኢየሱስ እናት›› ‹‹ሴቲቱ››እያሉ ሲጠርዋት ነው የምናየው፡፡ ሁሉም መጠሪያዎች የነቢያትን ትንቢት መፈጸም የሚያሳዩና የሥጋዌን ምጢር ያዘሉ ናቸውና፡፡ይህን የተረዱ ሊቃውንት‹‹እመ አምላክ፣ ወላዲተ አምላክ፣እመ ብርሃን ወዘተ…››እያሉ መጥራቻቸው ወንጌላውያንን አብነት አድርገውነገ ሥጋዌን ለመግለጽና ክብሯን ለመመስከር ነው፡፡

          እመቤታችን በኤልሳቤጥ ቤት ሆነውን ካየች በኋላ‹‹ለእኔ(በእኔ)ታላቅ ሥራን አድርጓልና ስም ቅዱስ ነው›› ስትል አመስግናለች፡፡ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስብሎ ማመስገን በዓለ መላእክት የተለመደ ነው፡፡የመላእክት እህት የሆነች እመቤታችንም ከነፍሷ የሆነ ምስጋናዋን በዚሁ ሰማያዊ በሆነ ምስጋና ገልጻለች፡፡ ይህም ከመላእክት ጋር የነበራትን የምስጋና ኅብረት ያሳያል፡፡ከዚህም በግላችንም ሆነ ለፍጥረተ ዓለም ለተደረገው የእግዚአብሔር የቸርነቱ ሥራ ማመስገን የተገባ መሆኑን ለሁላችን ትምህርት ትታልናለች፡፡

እመቤታችን ፈጣሪዋናአምላኳ እንዲሁም ልጇ የሆነውን እርሱን ማመስገን ብቻ ሳይሆን፤በእርሷ ላይ በተደረገው ድንቅ ነገር ትውልድ ሁሉ ሲያመሰግኗት ሲያደንቋ እንደሚኖሩም ገልጻለች፡፡በዚህም የተነሳ እውነተኛዋ የሐዋርያ ቤተክርስቲን ልዑል እግዚአብሔርን ከማመስገን ለጥቃ  እመቤታችንን በውዳሴ በቅዳሴ በማንሳት ታመሰግናለች፡፡ ልጆቿም በነገር ሁሉ በንጽሕናና በቅድስና በማጌጥ እናታቸውን ቅድስት ድንግል ማርያምን እንዲመስሉ ታስተምራለች፡፡ ቤተክርስቲያን በማኅሌቱ በቅዳሴው በሰዐታቱ በስብከቱና በትምህርቱ ሁሉ ደጋግማ እመቤታችንን የማንሳቷ ምስጢር በንጽሕናና በቅድስናዋ አብነት በመሆን በአማላጅነቷም ፍጹምነት ወደ እግዚአብሄር እቅፍ የምታደርሰን በመሆኗ ነው፡፡

ከጥንት ሲወርድ ሲወራረድ የመጣው ትክክለኛ ዶግማ ኖናና ትውፊት እንዳይበረዝ እዳይከለስ በማስተማር ጠብቃ ማቆየቷ የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያንን ከማንም በላይ ሐዋርያት ከጌታችን የተቀበሉት የጥንታዊውና የእውነተኛው ክርስትና የታመነችባለ አደራ ቤተ መዘክር ያደርጋታል፡፡

ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር!

                                               እንኳን ለጾመ ፍልሰታ ለማርያም በሰላም አደረሰን!

                                                                 ቀሲስ ታምራት ውቤ

ነሐሴ 2007 ዓ.ም


Leave a comment

Make sure you enter the (*) required information where indicated. HTML code is not allowed.

back to top

ጠቃሚ አድራሻዎች

መጻሕፍት ቢያነቧቸው

  • * ​ፍቅር 
  • ፍና ቅዱሳን
  • * የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ሕይወቱ እና ትምህርቱ 
  • * ዝጎራ