Login
Main menu

ትውልዱ ከእመቤታችን ምን ይማራል?

Index

 

2ኛ.ይማኖት፡- ከወላዲተ አምላክ ማርያም አንዱ የተማርነው ይማኖ ነው፡፡ከእርሷ በፊት ያልሆነ ከተፈጥሮ ርዓት የተለየ ያለወንድ ዘር መነስ እና በድንግልና መውለድ በመልአኩ ሲነገራትና ይህ ይሆን ዘንድ ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር የለም ሲላት ፈቃዷን በይማኖት ገልጣለች፡፡ ፍጹም እምነት ማለትም ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር የለም ብሎ ማመን ነው፡፡

በቃና ዘገሊላ ርግ ለልጇ የወይን ጠጅ ማለቁን ከነገረችው በኋላ ላገልጋዮች በፍጹም እምነት የሚላችሁን አድርጉ ብላቸዋለች፡፡ በዚያ ደቂቃ ለዚያ ሁሉ ርገኛ የሚሆን ወይን ከየት ያመጣል? ምን መፍትሄ ሊኖር ይችላል?የመሳሰሉት የጥርጥር ሀሳቦች በእርሷ ዘንድ አልነበሩም፡፡ ሁሉን ቻይ መሆኑን ከቀድሞም አውቃና አምና ትኖር ነበርና፡፡

ዛሬ ያለውለም አካሄድ በእምነት ካልሆነ ማሸነፍ አይቻልም፡፡ከተስፋ መቁረጥ የተነሳ ጨለማው የማያልፍ ደመናው የማይገ የሚመስላቸው ብዙዎች ይኖራሉ፡፡ እምነት ማለት በእግዚአብሔር ኃይል የማይቻለው ይቻላል ሆን የማይመስለው ይሆናል ብሎ ማመን ነው፡፡ የተፈጥሮ ህግ፣ አመክንዮ ወዘተ… እዚህ ቦታ የላቸውም፡፡ የእርሱ ሥራ ከዚህ ሁሉ በላይ ነውና፡፡

3ኛ. ፍጹም ታዛዥነት፡- እመቤታችን ፈቃዷ ሁሉ ለልጇ የተሰጠ ነበር፡፡ ከእርሱ የተለየ ሀሳብ ወይም ፈቃድ አልነበራትም፡፡ ራሷን ፈጽማ ለእግዚአብሔር ያስገዛች ብላቴና ስለነበረች የመልአኩን ብራት የተቀበ የእግዚአብሔር ፈቃድ እንዲፈጸም ራሷን በመስጠት ነው፡፡ ከቀደምት ነያት እግዚአብሔር ፈቃዱን ለመፈጸም ሲልካቸው ሲጠራቸው ምክንያት በማንሳት ወደኋላ ለማለት የሞከሩ ነበሩ፡፡ እግዚአብሔር ለሚጠራን አገልግሎት መማራት ክብር እንደሆነ ሁሉ ታላቅ ሸክምና ላፊነትም ነው፡፡ እመቤታችን ለእናትነት ስትመረጥ ታላቅ ክብር መሆኑ ቢታወቅም ‹‹በነፍስሽ ሰይፍ ያልፋል›› እስኪባል የደረሰ ታላቅ ላፊነትም ነበር፡፡ በፍጹም ታዛዥነትም እስከ ፍጻሜ ኃላፊነቷን ተወጥታለች፡፡ በመጨረሻም በመስቀል ላይ ሳለ በፈቃዱ ወደ እርሱ እስኪወስዳት ድረስ በዮሐንስ ዘንድ እንድትኖር ሲነግራት በጊዜው ወድቆባት ነበረ ነፍስን የሚወጋ ሀዘን ቃሉ ያላትን ታዛዥነት አልለወጠውም፡፡ 

4ኛ.ጥበብ መንፈሳዊ፡- እመ አምላክ ብራተ መልአክን በተቀበለችበት ወቅት ቅዱስ ገብርኤልን ትጠይቀው የነበሩ ጥያቄዎች ፍጹም ጥበብ መንፈሳዊ የተሞነበሩ፡፡ ከጉባዔ ያልዋሉ ምሥጢር ያላደላደሉ የመጽሐፍ ቅዱስ የከንፈር ወዳጆች የእመቤታችንን ጥያቄዎች የጥርጥር ያለማመን አድርገው ሲያቀርቡ እነሆ እንሰማቸዋለንእኒህ የወንጌሉ ምሥጢር የተከደነባቸው ናቸው፡፡እመቤታችን የጠየቀቻቸው ጥያቄዎች የተገቡና ነገረ ሥጋዌን የበለጠ እንዲብራራ ያደረጉ ናቸው፡፡ እመቤታችን ጥያቄዎቹን ባትጠይቅ ኖሮ፡-

    ሀ. ከእርሷ የሚወለደው ቅዱ የእግዚአብሔር ልጅ መሆኑ

    ለ. በድንግልናና ያለወንድ ዘር የተጸነሰና የሚወለድ መሆኑ

    ሐ. ለአበው በተሰጠው ተስፋና በትንቢ ነቢያት መረት የዳዊት ዘር መሆኑና የያዕቆብን ወገን ለዘላለም የሚገዛ መሆኑ፡

    መ. ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ነስቶ መለዱ በግብረ መንፈስ ቅዱስ መሆኑ

    ሠ. አብ ሊያፀናት ወልድ ለተዋሕዶ(ሥጋን ለመንሳት)መንፈስ ቅዱ ፍል ሊያዋሕድ እንደሚያድሩባት ተለይቶ ባልታወቀ ነበር

    ረ. የሚወለደው ሕጻን ስሙ ኢየሱስ እንደሚባልና ሕዝቡን ሁሉ ከጢአት ከመርገም ከፍዳ የሚያድናቸው መሆኑ

    ሰ. ራሷ እመቤታችን በንጽሕናና በቅድስናዋ ከሴቶች ሁሉ ተለይታ የከበረች መሆኗ

    ሸ. ነቢ ልዑል ዐርኩ ለመርዓዊ የተባለ የሐንስ መጥምቅ በእግዚአብሔር ድንቅ ተዐምራት ከዘካርያስና ከኤልሣቤጥ መፀነስ፤ኤልሳቤጥ በብፅዐት ብትሰውረውም የተገለጠ በእመቤታችን ጥያቄ ነው፡፡

          ብዙ ጠይቀን ጥቂት መልስ ለማናገኝ ለእኛ የጥያቄ አቀራረብን አቅል(ሥርዓት) እንረዳበት ዘንድ ታላቅ ትምህርት ነው፡፡በአግባቡ ያልቀረበ ጥያቄ መልስ አይኖረውምና፡፡

5ኛ. መናፍስትን መመር፡-‹‹መንፈስን ሁሉ አትመኑ፤ነገር ግን መናፍስት ከእግዚአብሔር ሆነው እንደሆነ መርምሩ››እንዲል፤እመቤታችን መልአኩ ተገልጦ የምስጋና ሰላም ባቀረበላት ጊዜ ወዲያውኑ አልተቀበለችውም፡፡መተርጉማን‹‹እናቴሔዋንን ያሳተ ሰይጣን…››ብላ አሰበች እንዲሉ ዛሬ ትንቢት ተናጋሪ፣ ራዕይ ተመልካችና ሕልም ሀላሚ በበዛበት ጊዜ፤ ብዙዎቻችንም በመናፍስት አራር የሚሆነውን ሳንመረምር በምናያቸው ድንቃ ድንቆች የሰዎችን እውነተኛነትና ቅድስና በምንመዝንበት ሰዓት ከተወዳጇ እናታችን እንዲህ ያለውን የመጠበቅ ጥንቃቄ ልንማር ያስፈልጋል፡፡1ዮሐ4፥1

6.ጭምትነት፡-እመቤታችን እንዴት ባለ ጭምትነት በንጽሕና በቅድስና እንዳደገች አባ ሕርያቆስ ሲናገር ‹‹ ኦ ድንግል አኮ በተላህዮ ዘልሕቂ ከመ አዋልደ ዕብራውያን እለ ያገዝፋ ክሣዶን አላ በቅድስና ወበንጽሕ ውስተ ቤተ መቅደስ ነበርኪ›› ድንግል ሆይ አንገታቸውን እንደሚያገዝፉ እንደ ዕብራውያን ሴቶች ልጆች በዋዛ ያደግሽ አይደለም በንጽሕና በቅድስና በቤተ መቅደስ ኖርሽ እንጂ በማለት ገልጿል፡፡ ከቅዱስ ገብርኤል ከኤልሳቤጥና ከጻድቁ ዮሴፍ ጋር በነበራት ጊዜ፤ ስምኦን አረጋዊ ጌታን ባቀፈውና ትንቢት በተናገረበት፤ በአሥራ ሁለት ዓመቱም በቤተ መቅደስ በጠፋባቸው ወቅት፤ እንዲሁም በጊዜ ስቅለቱ በደረሰባት ሀዘን ወዘተ…ጭምትነቷ በሚያስደንቅ ሁኔታ ታይቷል፡፡በእያንዳንዱ ሁኔታ ምታደርገው እንቅስቃሴም ሆነ ንግግር ፍጹም ጸጋን የተላበሰ ነበር፡፡ጥያቄዋ፣ ሰላምታዋ፣ ቅሬታዋንም ሆነ ሀዘኗን ትገልፅበት የነበረበት መንገድ በፍጹም ጭምትነት የተጌጠ ነበር፡፡ በመልአኩ እንደተነገራት በኤልሳቤጥም እንደተመሰከረላት የእስራኤል ተስፋ ከእርሷ እንደሚወለድ የታወቀ ቢሆንም ቸኩላ ይህን ምስጢር ለማንም አልገለጠችም፡፡ እርሱ በሚፈቅደው መንገድ ራሱን እስገልጥ በጭምትነት ጠበቀች እንጂ፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ ለጢሞዎስ በክርስቶስ ላመኑ ክርስቲያን ሴቶች መክር የሚገባውን ሲነግረው ‹‹…ሴቶች ጭምቶች፣የማያሙ፣ልከኞች፣በነገር ሁሉ የታመኑ ሊሆኑ ይገባቸዋል›› ብሎታል፡፡ 1ኛ ጢሞ3÷11 ቅምጥሊቱ ሴት ግን በሕይወቷ ሳለች የሞተች ናትና፡፡1ኛ ጢሞ5፥8 የክርስቲያን ሴቶች በራቸውም ሆነ በአነጋገራቸው በአለባበሳቸውም ሆነ በአካሄዳቸው ራሳቸውን በጭምትነት እንዲገልጹ ከእመቤታችን በላይ አርአያ ሊሆን የሚችል አሰጣቸውም፡፡


Leave a comment

Make sure you enter the (*) required information where indicated. HTML code is not allowed.

back to top

ጠቃሚ አድራሻዎች

መጻሕፍት ቢያነቧቸው

  • * ​ፍቅር 
  • ፍና ቅዱሳን
  • * የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ሕይወቱ እና ትምህርቱ 
  • * ዝጎራ