Login
Main menu

ታሪከ አበው: የአብርሃም የመጨረሻ ክፍል

Download
Name
Play
Size
Duration
download
አብርሃም
My Recording

72.1 MB
52:31 min

Read more...

ታሪከ አበው: ይስሐቅ

Download
Name
Play
Size
Duration
download
ይስሐቅ
yeneta

44.7 MB
55:51 min
download
ይስሐቅ ክፍል ሁለት
yeneta

86.3 MB
1:02:53 min
download
ይስሐቅ ክፍል ሦስት
yeneta

89.1 MB
1:04:52 min

Read more...

ትውልዱ ከእመቤታችን ምን ይማራል?

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን!

ትውልዱ ከእመቤታችን ምን ይማራል?

መግቢያ

‹‹ጐሥዐ ልብየ ቃለ ሠናየ›› በማለት አባ ሕርያቆስ በእመቤታችን ስም(ለእመቤታችን) በደረሰው ቁርባን ምስጋናው ስለ እመቤታችን ንጽሕናና ቅድስና፤ አካላዊቃልን በሥጋ  በመንፈስ ቅዱስ ግብር ለመውለድ መብቃት እንደቻለች፤ የአበው ተስፋ የነቢያትም ትንቢትና ምሳሌ በእርሱዋ እንዴት እንደተፈጸመ አምልቶ አስፍቶ ተናግሯል፡፡ ሊፈጽመውግን አልቻለም፡፡ ነቢዩ ዳዊት ‹‹ጐሥዐ ልብየ… ልቤ በጎ ነገርን አፈለቀ እኔ የንጉሥን ሥራ እናገራለሁ››፤ ብሎ ቅድመ ዓለም ያለ ፍጡራን አምላክ፣ ያለ ተገዢ ጌታ፣ ያለ ሎላልት ንጉሥ የሆነ፤ ድህረ ዓለም በማኅፀነ ማርያም በተዋህዶ ኋላም በመስቀል የነገሠ የእግዚአብሔርን ሥራ እናገራለሁ ብሎ ቢጀምር ሊፈጽመው እንዳልቻለ የአባ ሕርያቆስም እንዲሁ ነው፡፡መዝ 44፥1

ስለ ምሥጢረ ሥላሴ(ስለ እግዚአብሔር አንድነትና ልዩ ሦስትነት) በቅጥነተ ኅሊና ሊመረምሩ የወደዱ ብዙ ሊቃውንት፤ስለ አካላዊ ቃል በተለየ አካሉ ፍጹም ሰው መሆን የማይወሰነው መወሰኑ ርቀትን ከግዘፍ፣ኃይልን ከድካም፣ባዕልነትን ከንድየት፣ሕያውነትን ከመዋቲት ፍጹም በሆነ ተዋሕዶ ሳይቀላቀሉ ሳይለያዩ ሳይጠፋፉ አንድ ማድረግ፤ ጉምቱ ጉምቱ መንፈሳውያን ሊቃውንት ጠንቅቀው ሊጽፉ የሞከሩ ቢሆንም አንዳቸውም ግን ይህን ማድረግ ሳይቻላቸው ድካማቸው ስዒን በወለደው አንክሮ ተደምድሟል፡፡

የጌታ እግዚብሔር ባሕርይ የመድኃኒታችንንም ሰው የመሆን ምሥጢር ጠንቅቆ ፈፅሞ መናገር እንዳይቻል፤ የአብ ሙሽራ የወልድ ማደሪያ የመንፈስ ቅዱስ ንጽሕት አዳራሽ ስለሆነች ስለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም በእርሷ ስለተደረገ ነገርና ስለ ክብሯ ጠንቅቆ ፈጽሞ መናገር አይቻልም፡፡

‹‹ነኪር ነገሩ በእንቲአኪ ሀገረ እግዚአብሔር›› እንዳለ ነብዩ ዳዊት የእግዚአብሔር ከተማ ሆይ በአንቺ የተከበረ(ድንቅ) ነገር ይባላል ሲል ነው፡፡ቃሉ ቃለ አንክሮ ነው፡፡‹‹ድንቅ›› የሚለው ቃ አንክሮ ከአእምሮአችን በላይ ለሆነ የተከተተ መግለጫ ልንሰጠው ለማንችለው ጉዳይ የምንጠቀምበት ነው፡፡እመቤታችን ብሥራተ መልአኩን ከተቀበለች በኋላ ‹‹እስመ ገብረ ሊተ ኃይለ ዐቢያተ››አብ ቢሉ በልጁ ወልድ ቢሉ በሥልጣኑ ምድራዊ ባይደ ሰማያዊ፤ ተፈጥሯዊ ባይደለ አምላካዊ፤ ጊዜያዊ ያይደለ ዘላለማዊ ታላቅ ሥራን በእኔ አድርጓል ብላ መስክራለች፡፡መዝ 86፥3 ፤ሉቃ 1፥49

          እንዚራ መንፈስ ቅዱስ የተባለ ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ ስለ እመቤታችን በጻፈው ድርሰቱ በብዙ ሕብረ አምሳል እየመሰለ ሲያወድሳት ቢቆይም የእርሷን ክብርና ገናናነት ተናግሮ መፈጸም እንደማይቻል ከተረዳው በመንፈስ ቅዱስ የተቃኘ ሰውነቱ‹‹ኑ ዘይክል ነቢ ዕበየኪ ወአልቦ ዘይመስል ኪያኪ›› ትርጉም ‹‹ክብርሽን ተናግሮ መፈጸም የሚችል ማነው? አንቺን የሚመስልሽ የለምና››ሲል መልካም ነገርን አፍልቋል፡፡

          የምሥጋና አባቱ(መምህሩ)ነዩ ዳዊት ስለ ጌታ እግዚአብሔር‹‹መኑ ይመስለከ እም አማልክት እግዚኦ›› ‹‹አቤቱ ከአማልክት አንተን የሚመስልህ ማነው?›› ብሎ የልዑሉን ገናናነት እንደተናገረ፤ ከአማልክት የሚተካከለው ያይደለ የሚቀርበው፤የሚቀርበው ያይደለ የሚመስለው የሌለ የልዑሉ ዙፋን፤እርሱን በማኅፀኗ ተሸክማ በሥጋ ወልዳ ዓለማትን በረቂቅ በግዘ የሚመግበው ጡቶቿን አጥብታ ያሳደገች የእርሷም ክብር ገናንነት መናገር አይቻልም ሲል በምሥጢር መስሎታል፡፡ውዳሴ ማርያም ዘዓርብ

ጨምሮም ‹‹ዕበያ ለድንግል ኢይትከሀል ለተነግሮ እስመ እግዚእ ረያ›› የድንግል ክብሯ ጠንቅቆ ይነገር ዘንድ አይቻልም ጌታ መርጧታልና፡፡አብ ቢሉ ለልጁ ማደርያ እንድትሆን ወልድ ቢሉ ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ነሥቶ ከእርሷ ሰው ይሆን ዘንድ መርጧታልና፡ መምረጡንም ቅድመ ሥጋዌ ቢሉ በነቢያት ትንቢት፤ ጊዜ ጋዌ ሉ በመልክ ብራት፤ ድኅረ ሥጋዌ ቢሉ ሥጋን ነስቶ በመታየት፣ በሐዋርያት ትምህርት፣ በሊቃውንት መጻሕፍት አስረድቶናል፡፡ውዳሴ ማርያም ዘሠሉስ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤ/ክ ምዕመናን፤ እንዲሁም በእምነት በቀኖና የሚመስሏቸው ሌሎች የአኃት አብያተ ክርስቲያናት ምዕመናን ዳዊት በመዝሙሩ‹‹ወዘሕጎ ያነብብ መዐልተ ወሌሊተ ወይከውን ከመ ዕፅ እንተ ትክልት ኀበ ሙሐዘ ማይ፤እንተ ትብ ፍሬሃ በበጊዜሃ ወቈፅላኒ ኢይትነገፍ›› እንዳለ የነያትን ትንቢት፣የሐዋርያትን ትምህርት፣ የሊቃውንትን የትርጓሜ ድርሳናት፣ ከንፁሕ ምንጭ ስለ አምላካቸው ታላቅነት፤ ስለ እመቤታችንም ንፅሕና ቅስና ክ አማላጅነት ሲጠጡ በመኖራቸው ልምላሜ ነፍስ ሳይለያቸው ሥራ ሊሠሩ በተሰጣቸው ጊዜ የንስሐ ፍሬ የመንፈስ ፍሬ በማፍራት በትሩፋት ላይ ትሩፋት እየጨመሩ የእርሷን ጸጋ ክንፈ ረድዔት በማድረግ እንደ ንስር በመንፈሳዊ ሕይወትና እውቀት ሲመጥቁ ይታያሉ፡፡መዝ 1፥2-3

ክርስቲያን ለመባልና የልጅነትን ክብር ለማግኘት የቻልነው አካላዊ ቃል ከእመቤታን ተ  የቤዛነትን ሥራ በመፈጸም ዓለምን ካዳነ በኋላ ነው፡፡‹‹በስሙ ለሚያምኑ የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣን ሰጣቸው›› እንዲል፡፡ ወረደ ተወለደ መከራን ተቀበለ ተሰቀለ ሞተ ተነዐረገ ዳግመኛ በሕያዋንና በሙታን ለመፍረድ ይመጣል ብሎ ሥጋን ተዋሕዶ በፈፀመው ሥራና ስመ ሥጋዌውን ስመ ሥርየት ስመ ድኅነት ነው በማለት ማመን ነው፡፡ይህ ሁሉ የተፈፀመ ከእርሷ በነሳው ሥጋ ነው ብሎ የሚያም በነገረ ድኅነት ውስጥ ያለውን የእመቤታችንን ሱታፌ መገንዘብ አይሳነውም፡፡


 

          በኦሪት ጽላት ያደረበት(የተቀመጠበት)ታቦት በሚታይ ገንዘብ የእስራኤል ዘሥጋ የአምልኮታቸው ማዕከል ነበር፡፡ እግዚአብሔርም ቃሉን የሚያሰማቸው በታቦቱ ላይ በመገለፅ ነበር፡፡ እስራኤል ታቦቱን ይዘው ባህር ተከፍሎላቸው ቅጥር ፈርሶላቸው ጠላት ጠፍቶላቸው ምደረ ስት ከነዓንን ወርሰዋል፡፡ታቦት የእመቤታችን ጽላት የጌታ ምሳሌ መሆኑ በብዙ መተርጉማን የተብራራ ነው፡፡ የአዲስ ኪዳን ቤተ ክርስቲያንም የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን አዳኝነትና የእመቤታችንን ምልጃ ማዕከል አድርጋ አምልኮዋን ትፈጽማለች፡፡ ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም የጌታችንን መወለድ በልባቸው ይዘው ያመኑ፤ በአፋቸውም የእርሱን አምላክነት የእርሷን ወላዲተ አምላክነት የሰከሩ ምዕመናን በጥምቀት በሚገኝ ልጅነት ጥቅመ ኃጢአት ፈርሶላቸው ዲያብሎስን ድል ነስተው ርስ መንግሥተ ሰማያትን ለመውረሳቸው ምሳሌ ነበር፡፡

ቅድስት ድንግል ወላዲተ አምላክ ማርያምን አልቦ (ያገለለ) ክርስትና የለም፡፡በዚህ የተቃኘ ትምህርትም ከአባቶቻችን ከሐዋርያትና ከሊቃውንት የተገኘም አይደለም፡፡ ወንጌላውያኑም እመቤታችን በወንጌል በነገረ ድኅነት የነበራትን ሱታፌ በግልጽ ጽፈውታል፤ከጽን እስከ በዓለ ጵራቅሊጦስ፡፡ ጌታችን ካረገ በኋላ እንኳ ሐዋርያት እርሷን  እንደ ታቦት በመካከላቸው አድርገው ይጸልዩ ነበረ ፡፡ጸሐፊው‹‹የኢየሱስም እናት በመካከላቸው ነበረች›› ብሎ የጻፈ ያለ ምክንያት አይደለም፡፡

ጌታችን ልጅነትን የምናገኝበትን ሥርዓ ጥምቀት አስቀድሞ በግብር ፈፅሞ ምሳሌ በመሆን ኋላ በቃ ከውኃና ከመንፈስቅዱስ ካልተወለዳችሁ ወደ እግዚአብሔር መንግስት ልትገቡ አይቻላችሁም እንዳለ፤ በመስቀሉ ላይ በዮሐንስ አማካኝነት በእርሱ ለሚያምኑ ሁሉ‹‹እነኋት እናትህ›› ‹‹እነሆ ልጅሽ›› ብሎ በቃሉ እናት አድርጎ ከመስጠቱ በፊት ከእርሷ በመወለዱ ልጆቿ አድርጎናል፡፡ ሊቃውንትም የእግዚአብሔር የባሕርይ ልጁ በመሆኑ እኛን በጸጋ የእግዚአብሔር ልጆች አደረገን ‹‹ወደ አባቴ ወደ አባታችሁ. . .›› እንዲል፤ ከድንግሊቱም ተወለዶ የድንግሊቱ ልጆች አደረገን ብለው አመስጥረውታል፡፡የዮሐንስ አፈወርቅ የማቴዎስ ወንጌል ትርጓሜ ማቴ1፥25-ፍጻሜ

ጌታ ቅድመ ዓለም አካል ዘእምአካል ባህርይ ዘእምባህርይ ከአብ እንደተወለደ፤ ድኅረ ዓለም ደግ ከእመቤታችን ፍጹም የሰውን ባህርይ በመያዝ በግዘፍ አካል ነስቶ ተወልዷል፡፡‹‹ንሕነ አባላቲሁ ለክርስቶስ››እ የክርስቶስ ብልቶቹ(አካሉ)ነን እንዲል ቅዱስ ጳውሎስ በምሥጢር የክርስቶስ አካሉ የምንባል ክርስቲያኖች ሁሉ ከእርሷ ተወልደናል፤ እናትነቷም ተሰጥቶናል፡፡ ‹‹እምነ ጽዮን ይብል ሰብእ ወብእሲ ተወልደ በውስቴታ›› ‹‹ሰው እናታችን ጽዮን ይላል ከእርሷ ሰው ተወልዷልና›› ዳለ ክቡር ዳዊት ከአዳም በሥጋ የተወለደ ሁሉ እንደሞተ፤ ከእርሱ(ከክርስቶስ) በመንፈስ የሚወለድ ሁሉ ለዘላለም በሕይወት እንዲኖር ከእርሷ ተወልዷልና ሰው እመቤታችንን ጸወነ ሥጋ ጸወነ ነፍስ(የነፍሳችንና የሥጋችን መጠጊያ መጽናኛ) እናታችን ሲላት ይኖራል ሲል የተናገረው ሁሉ በዚህ ተፈጽሟል፡፡1ቆሮ6፥15፤1ቆሮ12፥12-27፤መዝ86፥5

እመቤታችን በክርስትና ካላት ቦታ በትንሹ ይህ ካልን በልጇ አምን ክርስቲያን የተባልን ሁላችን ከእናትነቷ ምን ተምረናል? በወንጌል ከተገለጠው የእመቤታችን ሕይወት ምን ወስደናል? በእርግጥስ እንደ እናትነቷ እኛ የክርስትና ሕይወት ለእርሷ ደስታ የሚሆን ነው? የሚለውን ማንሳት ያስፈልገናል፡፡

ይህንን እንድናነሳ ያስገደደን በአብዛኛው ስለ እርሷ በማስተማር እንጂ ከእርሷ ፍጹም ልዩና የተቀደሰ ሕይወት ስንማር አንታይምና ነው፡፡ከእመቤታችን ሕይወት ልንወርስ የሚገቡንን  አርአያ ቅድስና (መልካም ነገሮች) መንፈስ ቅዱስ በዘመናት በሊቃውንት አንደበት በቅዱሳን ሕወት አድሮ እንዳስተማረን ሁሉ ከእርሱ የተቀበልነውን እንዲሁ እናቀብላለን፡፡

1ኛ. ትህትና፡- በእመቤታችን ሕይወት የምናየው በቃላት ከመገለጽ በላይ የሆነ ትኅትና ነው፡፡ ሊቃውንት ወትሮም እመቤታችን መጽሐፈ ኢሳያስን ስታነ‹‹እነሆ ድንግል ትጸንሳለች ወንድ ልጅም ትወልዳለች ስሙን አማኑኤል ብላ ትጠራዋለች›› ብሎ ከተናገረው ብትደርስ እኔ በሆንኩ አላለችምከዚች ድንግል ደርሼ ወጥቼ ወርጄ ባገለገልኳት አለች እንጂ፡፡ ኢሳ7፥14

ዛሬ ክብርን ሁሉ የከፍታ ወንበርን ሁሉ ለራሱ የሚመኝ እንጂ ለሀገር ለቤተክርስቲያን እንዲህ የሚራ ተነስቶ እኔ አገልጋዩ ሆኜ ባለፍኩ የሚል ማግኘት አስቸጋሪ በሆነበት ጊዜ ይህን የእመቤታችንን የትኅትና ሕይወት ማስተዋል ያስፈልገናል፡፡ተመርጠው ለክብር የሆኑትንም ስናይ ቀርቦ ማገልገል እንጂ መተቸት ለውጥ አያመጣም፡፡ ዛሬ ሁላችን የምንጨነቅ ሌላውን ስለመለወጥ እንጂ ስለራሳችን መለወጥ አይደለም፡፡

የእመቤታችን ትኅትና በመልአኩ ብስራትም ተገልጸ_ል፡፡ ያንቺ ጽንስ እንደ ሌሎች ሴቶች አይደለም ካንቺ የሚወለደው ቅዱሱ የእግዚአብሔር ልጅ ነው ባላት ሰዓት‹‹እነሆ የጌታ አገልጋ (ገረዱ)እንደ ቃልህ ይሁንልኝ›› በማለቷ ታውቋል፡፡ እናቱ ትሆኛለሽ ሲላት ለልጇ አገልጋዩ መሆንዋን በመግለጽ ነበር ትኅትናዋን ያሳየች፡፡

ጌታ በመስቀል ሳለ ለዮሐንስ ‹‹እነኋት እናትህ››ለእመቤታችንም ‹‹እነሆ ልጅሽ›› ብሎ ሲያረካክባቸው፤ ከጌታ ጋር ኖሬ አገልጋይ፣ ከመምህር ጋር ኖሬ ከደቀመዝሙር፤ ከፈጣሪ ጋር ኖሬ ከፍጡር  አላለችም ዮሐንስ ወደ ቤቱ ሲወስዳት በትኅትና ተቀለች እንጂ፡፡ ስንቶቻችን ይሆን ከታናናሾቻችን ጋር እነርሱን መስለን መኖር የምንችል? ከታላላቆች ጋርማ ማንነታችንን ሸጠን ክብራችንን ጥለን እምነታችንን ሰውተን አንገታችንን እንደከዘራ ቆልምመን መኖርን እናውቅበታለን፡፡ ለፍርፋሪ ስንል!!!


 

2ኛ.ይማኖት፡- ከወላዲተ አምላክ ማርያም አንዱ የተማርነው ይማኖ ነው፡፡ከእርሷ በፊት ያልሆነ ከተፈጥሮ ርዓት የተለየ ያለወንድ ዘር መነስ እና በድንግልና መውለድ በመልአኩ ሲነገራትና ይህ ይሆን ዘንድ ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር የለም ሲላት ፈቃዷን በይማኖት ገልጣለች፡፡ ፍጹም እምነት ማለትም ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር የለም ብሎ ማመን ነው፡፡

በቃና ዘገሊላ ርግ ለልጇ የወይን ጠጅ ማለቁን ከነገረችው በኋላ ላገልጋዮች በፍጹም እምነት የሚላችሁን አድርጉ ብላቸዋለች፡፡ በዚያ ደቂቃ ለዚያ ሁሉ ርገኛ የሚሆን ወይን ከየት ያመጣል? ምን መፍትሄ ሊኖር ይችላል?የመሳሰሉት የጥርጥር ሀሳቦች በእርሷ ዘንድ አልነበሩም፡፡ ሁሉን ቻይ መሆኑን ከቀድሞም አውቃና አምና ትኖር ነበርና፡፡

ዛሬ ያለውለም አካሄድ በእምነት ካልሆነ ማሸነፍ አይቻልም፡፡ከተስፋ መቁረጥ የተነሳ ጨለማው የማያልፍ ደመናው የማይገ የሚመስላቸው ብዙዎች ይኖራሉ፡፡ እምነት ማለት በእግዚአብሔር ኃይል የማይቻለው ይቻላል ሆን የማይመስለው ይሆናል ብሎ ማመን ነው፡፡ የተፈጥሮ ህግ፣ አመክንዮ ወዘተ… እዚህ ቦታ የላቸውም፡፡ የእርሱ ሥራ ከዚህ ሁሉ በላይ ነውና፡፡

3ኛ. ፍጹም ታዛዥነት፡- እመቤታችን ፈቃዷ ሁሉ ለልጇ የተሰጠ ነበር፡፡ ከእርሱ የተለየ ሀሳብ ወይም ፈቃድ አልነበራትም፡፡ ራሷን ፈጽማ ለእግዚአብሔር ያስገዛች ብላቴና ስለነበረች የመልአኩን ብራት የተቀበ የእግዚአብሔር ፈቃድ እንዲፈጸም ራሷን በመስጠት ነው፡፡ ከቀደምት ነያት እግዚአብሔር ፈቃዱን ለመፈጸም ሲልካቸው ሲጠራቸው ምክንያት በማንሳት ወደኋላ ለማለት የሞከሩ ነበሩ፡፡ እግዚአብሔር ለሚጠራን አገልግሎት መማራት ክብር እንደሆነ ሁሉ ታላቅ ሸክምና ላፊነትም ነው፡፡ እመቤታችን ለእናትነት ስትመረጥ ታላቅ ክብር መሆኑ ቢታወቅም ‹‹በነፍስሽ ሰይፍ ያልፋል›› እስኪባል የደረሰ ታላቅ ላፊነትም ነበር፡፡ በፍጹም ታዛዥነትም እስከ ፍጻሜ ኃላፊነቷን ተወጥታለች፡፡ በመጨረሻም በመስቀል ላይ ሳለ በፈቃዱ ወደ እርሱ እስኪወስዳት ድረስ በዮሐንስ ዘንድ እንድትኖር ሲነግራት በጊዜው ወድቆባት ነበረ ነፍስን የሚወጋ ሀዘን ቃሉ ያላትን ታዛዥነት አልለወጠውም፡፡ 

4ኛ.ጥበብ መንፈሳዊ፡- እመ አምላክ ብራተ መልአክን በተቀበለችበት ወቅት ቅዱስ ገብርኤልን ትጠይቀው የነበሩ ጥያቄዎች ፍጹም ጥበብ መንፈሳዊ የተሞነበሩ፡፡ ከጉባዔ ያልዋሉ ምሥጢር ያላደላደሉ የመጽሐፍ ቅዱስ የከንፈር ወዳጆች የእመቤታችንን ጥያቄዎች የጥርጥር ያለማመን አድርገው ሲያቀርቡ እነሆ እንሰማቸዋለንእኒህ የወንጌሉ ምሥጢር የተከደነባቸው ናቸው፡፡እመቤታችን የጠየቀቻቸው ጥያቄዎች የተገቡና ነገረ ሥጋዌን የበለጠ እንዲብራራ ያደረጉ ናቸው፡፡ እመቤታችን ጥያቄዎቹን ባትጠይቅ ኖሮ፡-

    ሀ. ከእርሷ የሚወለደው ቅዱ የእግዚአብሔር ልጅ መሆኑ

    ለ. በድንግልናና ያለወንድ ዘር የተጸነሰና የሚወለድ መሆኑ

    ሐ. ለአበው በተሰጠው ተስፋና በትንቢ ነቢያት መረት የዳዊት ዘር መሆኑና የያዕቆብን ወገን ለዘላለም የሚገዛ መሆኑ፡

    መ. ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ነስቶ መለዱ በግብረ መንፈስ ቅዱስ መሆኑ

    ሠ. አብ ሊያፀናት ወልድ ለተዋሕዶ(ሥጋን ለመንሳት)መንፈስ ቅዱ ፍል ሊያዋሕድ እንደሚያድሩባት ተለይቶ ባልታወቀ ነበር

    ረ. የሚወለደው ሕጻን ስሙ ኢየሱስ እንደሚባልና ሕዝቡን ሁሉ ከጢአት ከመርገም ከፍዳ የሚያድናቸው መሆኑ

    ሰ. ራሷ እመቤታችን በንጽሕናና በቅድስናዋ ከሴቶች ሁሉ ተለይታ የከበረች መሆኗ

    ሸ. ነቢ ልዑል ዐርኩ ለመርዓዊ የተባለ የሐንስ መጥምቅ በእግዚአብሔር ድንቅ ተዐምራት ከዘካርያስና ከኤልሣቤጥ መፀነስ፤ኤልሳቤጥ በብፅዐት ብትሰውረውም የተገለጠ በእመቤታችን ጥያቄ ነው፡፡

          ብዙ ጠይቀን ጥቂት መልስ ለማናገኝ ለእኛ የጥያቄ አቀራረብን አቅል(ሥርዓት) እንረዳበት ዘንድ ታላቅ ትምህርት ነው፡፡በአግባቡ ያልቀረበ ጥያቄ መልስ አይኖረውምና፡፡

5ኛ. መናፍስትን መመር፡-‹‹መንፈስን ሁሉ አትመኑ፤ነገር ግን መናፍስት ከእግዚአብሔር ሆነው እንደሆነ መርምሩ››እንዲል፤እመቤታችን መልአኩ ተገልጦ የምስጋና ሰላም ባቀረበላት ጊዜ ወዲያውኑ አልተቀበለችውም፡፡መተርጉማን‹‹እናቴሔዋንን ያሳተ ሰይጣን…››ብላ አሰበች እንዲሉ ዛሬ ትንቢት ተናጋሪ፣ ራዕይ ተመልካችና ሕልም ሀላሚ በበዛበት ጊዜ፤ ብዙዎቻችንም በመናፍስት አራር የሚሆነውን ሳንመረምር በምናያቸው ድንቃ ድንቆች የሰዎችን እውነተኛነትና ቅድስና በምንመዝንበት ሰዓት ከተወዳጇ እናታችን እንዲህ ያለውን የመጠበቅ ጥንቃቄ ልንማር ያስፈልጋል፡፡1ዮሐ4፥1

6.ጭምትነት፡-እመቤታችን እንዴት ባለ ጭምትነት በንጽሕና በቅድስና እንዳደገች አባ ሕርያቆስ ሲናገር ‹‹ ኦ ድንግል አኮ በተላህዮ ዘልሕቂ ከመ አዋልደ ዕብራውያን እለ ያገዝፋ ክሣዶን አላ በቅድስና ወበንጽሕ ውስተ ቤተ መቅደስ ነበርኪ›› ድንግል ሆይ አንገታቸውን እንደሚያገዝፉ እንደ ዕብራውያን ሴቶች ልጆች በዋዛ ያደግሽ አይደለም በንጽሕና በቅድስና በቤተ መቅደስ ኖርሽ እንጂ በማለት ገልጿል፡፡ ከቅዱስ ገብርኤል ከኤልሳቤጥና ከጻድቁ ዮሴፍ ጋር በነበራት ጊዜ፤ ስምኦን አረጋዊ ጌታን ባቀፈውና ትንቢት በተናገረበት፤ በአሥራ ሁለት ዓመቱም በቤተ መቅደስ በጠፋባቸው ወቅት፤ እንዲሁም በጊዜ ስቅለቱ በደረሰባት ሀዘን ወዘተ…ጭምትነቷ በሚያስደንቅ ሁኔታ ታይቷል፡፡በእያንዳንዱ ሁኔታ ምታደርገው እንቅስቃሴም ሆነ ንግግር ፍጹም ጸጋን የተላበሰ ነበር፡፡ጥያቄዋ፣ ሰላምታዋ፣ ቅሬታዋንም ሆነ ሀዘኗን ትገልፅበት የነበረበት መንገድ በፍጹም ጭምትነት የተጌጠ ነበር፡፡ በመልአኩ እንደተነገራት በኤልሳቤጥም እንደተመሰከረላት የእስራኤል ተስፋ ከእርሷ እንደሚወለድ የታወቀ ቢሆንም ቸኩላ ይህን ምስጢር ለማንም አልገለጠችም፡፡ እርሱ በሚፈቅደው መንገድ ራሱን እስገልጥ በጭምትነት ጠበቀች እንጂ፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ ለጢሞዎስ በክርስቶስ ላመኑ ክርስቲያን ሴቶች መክር የሚገባውን ሲነግረው ‹‹…ሴቶች ጭምቶች፣የማያሙ፣ልከኞች፣በነገር ሁሉ የታመኑ ሊሆኑ ይገባቸዋል›› ብሎታል፡፡ 1ኛ ጢሞ3÷11 ቅምጥሊቱ ሴት ግን በሕይወቷ ሳለች የሞተች ናትና፡፡1ኛ ጢሞ5፥8 የክርስቲያን ሴቶች በራቸውም ሆነ በአነጋገራቸው በአለባበሳቸውም ሆነ በአካሄዳቸው ራሳቸውን በጭምትነት እንዲገልጹ ከእመቤታችን በላይ አርአያ ሊሆን የሚችል አሰጣቸውም፡፡


 

7. በራዊ ሕይወት፡- እመብርሃን ቅድስት ድንግል ማርያም የኤልሳቤጥንመነስ ከመልአኩ እንደሰማች ፈጥና ነው ወደ ኤልሳቤጥ የሄደችው፡፡ ያቺ እግዚአብሔርን በመፍራት የምትኖር የካህን ሚስት ስለቷ ተሰምቶ በመልአክራት ወንድ ልጅ መነሷን ስትሰማ ደስታዋን ለመካፈል አልዘገየችም፡፡ በሰው ሀዘን ተደስቶ በባልንጀራው ደስታ የሚከፋ በበዛበት በዚህ ክፉ ዓለም የእርሷን አርአያ መከተል ምንኛ መቀደስ ነው፡፡ቅዱስ ጳውሎስም ‹‹ደስ ከሚላቸው ጋር ደስ ይበላችሁ፣ሚያዝኑ ጋር አልቅሱ››ያለ የሰውን ስሜት በቅንነት መካፈልክርስቲያናዊ ምግባር በመሆኑ ነው፡፡ሮሜ 12፥15፤ ሉቃ 1፥57-65

          ከእግዚአብሔር የሆነን ነገር ደግሞ የሰዎቹን ደስታ ከመካፈል ባለፈ ማድነቅ ይገባል፡፡ለኤልሳቤጥ ከእግዚአብሔር እንደሆነው ሁሉ ለሕዝቡ ጥቅም ከእግዚአብሔር የሆነ ስጦታ(ጸጋ) የተሰጣቸው ስንመለከት

ሀ. እግዚአብሔር በእርሱ አድሮ ስለሠራው ድንቅ ሥራ

ለ.እግዚአብሔር በእርሱ አድሮ ሕዝቡን ስለመጥቀሙ

ሐ.በዘመናችንም ዓይኖቻችን የእርሱን ድንቅ ሥራ በማየታቸው ልንደሰት ይገባናል፡፡ ከእግዚአብሔር በሆነ ጸጋ መቅናት፤ሰዎቹ ሩት ሥራ እንቅፋት መሆን ከእግዚአብሔር ጠላቶች ጋር መሰለፍ ነው፡፡

8. ድንግልና፡- የእመቤታችን ድንግልና፡-

ሀ. በሥጋ በኅሊና በመሆኑ( ድንግል በኅሊናኪ ወድንግል በሥጋኪ) እንዲል

ለ.ሕዋቶቿ በሙሉ የተጠበቁ መሆናቸው ማለት የኃጢአት መግያ ከሆኑት ከርዕይ ከሰሚዕ ከገሢሥ ከአንዎ የተጠበቀች መሆኗ( ከማየት፣ከመስማት፣ከመዳሰስ፣ከማሽተት)

ሐ.ቅድመ ጸኒስ ጊዜ ጸኒስ ድኅረ ጸኒስ ፤ቅድመ ወሊድ ጊዜ ወሊድ ድኅረ ወሊድ ድንግልናዋ ለቅጽበት ያልተለወጠ መሆኑ(ድንግልናዋ እናት በመሆኗ ያልተለወ መሆኑ)ልዩ ያደርጋታል፡፡ይህ ለሌሎች ሴቶች አይቻልምና‹‹ከሴቶች ተለይተሸ››ያሰኛት ቅሉ አንዱ ይህ ነው፡፡

          በተፈጥሮ ርዓት አንዲት ሴት ሙሽራዋን እስክታገኝ(እስኪመጣ)ራሷን በመግዛት እንደምትጠብቅ፤ ያ ካልሆነ ግን ከክብር እንደምታንስ በመንፈሳዊው ይወትም ነፍሳችንን በኃጢት ከክብር ከማነስ ጠብቀን ድንግልና የተባለ ልጅነታችንን በሃይማኖት በምግባርሙሽችን የሆነው ክርስቶስ እስኪመጣ እንጠብቃለን፡፡

ለእርሱ ለክርስቶ የሸለመች ሙሽራ ሆነን እንዴት ባለ የነፍስ ቅድስና መጠበቅ እንዳለብን የተሰጠችን ሕያው ምሳሌ ደግሞ እመቤታችን ነች፡፡ በእርሷ በአካል ያደረ በእኛ በጸጋ ያድርብናልና፡፡የዮሐ.ራዕ 21፥2

9.ጸሎት፡- እመቤታችን የመልአኩን ብሥራት የኤልሳቤጥንና የዮሐንስን ምሥክርነት ከተቀበለች በኋላ የተናገረችው ጸሎት ዘመናት በአላውያን ነገሥት በአረማውያን እንዲሁም በመናፍቃን የተነሣባትን የጥፋት ማዕበል ለመሻገር ለቤተክርስቲያን ጉልበት የሆነ ነው፡፡ጸሎቷም ምን ያህል በቅዱሳት መጽሐፍት እውቀት የበለጸገ የልዑሉንም ሥራ በማስተዋል የከበረ መሆኑ ተገልጦ የሚታይ ነው፡፡  ፍጹም በነፍሷ ለእግዚአብሔር ያላትን ክብር፣ ትኁታኑን ማይረሳ መሆኑን፤ ቅድስናውን፣ እውነተኛ ፈራጅ መሆኑን፣ለሚፈሩት የሰጣቸውን ቃል ኪዳን የማይረሳና ምህረቱም ለልጅ ልጅ መሆኑን የገለጠ ነው፡፡በከንፈ እግዚአብሔርን የሚያከብሩና በነፍሳቸው ልዑሉን የሚፈሩ የጸሎታቸው ልዩነት ለማነጻጸር ከሚቻል በላይ ነው፡፡ ጸሎተ ማርያም ዛሬም ድረስ በቤተክርስቲያን ለካህናት ሞገስ ለሕሙማን ፈውስ፤ ለሀገር ሰላም ለርኁባን ምግብ፤ለመምህራን ጽናት ለደቀመዛሙርት እውቀት የሆናቸው ለዚህ ነው፡፡ሐዋርያትም በጸሎታቸው ወቅት እርሷን ይዘው መጸለያቸው የጸሎታቸው ምላሽ ይፈጥን ዘንድ ነው፡፡የእርሷ ጸሎት ተሰሚ ጉዳይ ፈጻሚ መሆኑን በቃና ርግ በግልፅ ማት ይቻላል፡፡ ‹‹የወይን ጠጅ እኮ የላቸውም››ብላ ለልጇ ከነገረችው በኋላ ድጋሚ መጠየቅ አላስፈለጋትም ‹‹የሚላችሁን አድርጉ›› አለች እንጂ፡፡ ደራሲ‹‹አልቦ ጸሎት ወአልቦ ትንባሌ እንሌኪ ድንግል ዘየዐርግ ሉዐሌ››ያለ ይህን ማስተዋል በመቻሉ ነው፡፡በመሆኑም እመቤታችንን ሳትይዝ ጸሎት ልመና አቀርባለሁ የምትል ቤተክስቲያን ብትኖር እርሷ ሐዋርያት የሰበሰቧት ቤተክርስቲያን አለመሆኗ በዚህ ይታወቃል፡፡

0. ምስጋና፡- እመቤታችን በእርሷ ላይ ይሆን ዘንድ ልዑሉ የፈቀደው ከሆነ በኋላ ይን የተረዱ እነ ኤልሳቤጥ ተፀውዖ ስሟ ማርያም ብለው መጥራታቸውን እንደማይገባ ድፍረት አድርገውስለቆጠሩት፤ የእርሷም ከቤታቸው ጣሪያ በታች መግባት የተገባቸው እንዳልሆነ ስለተረዱት‹‹የጌታዬ እናት ወደ እኔ ትመጣ ዘንድ እንዴት ይሆንልኛል?››በማለት ክብሯን ገልጠው መሰከሩ፡፡እቤታችን ጌታን ፀንሳ ከወለደች በኋላ በወንጌል እንዲሁ ‹‹ማርያም›› ተብላ ስትጠራ አናገኝም፡፡ወንጌላውያኑ ሁሉ ‹‹የሕጻኑ እናት›› ‹‹የኢየሱስ እናት›› ‹‹ሴቲቱ››እያሉ ሲጠርዋት ነው የምናየው፡፡ ሁሉም መጠሪያዎች የነቢያትን ትንቢት መፈጸም የሚያሳዩና የሥጋዌን ምጢር ያዘሉ ናቸውና፡፡ይህን የተረዱ ሊቃውንት‹‹እመ አምላክ፣ ወላዲተ አምላክ፣እመ ብርሃን ወዘተ…››እያሉ መጥራቻቸው ወንጌላውያንን አብነት አድርገውነገ ሥጋዌን ለመግለጽና ክብሯን ለመመስከር ነው፡፡

          እመቤታችን በኤልሳቤጥ ቤት ሆነውን ካየች በኋላ‹‹ለእኔ(በእኔ)ታላቅ ሥራን አድርጓልና ስም ቅዱስ ነው›› ስትል አመስግናለች፡፡ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስብሎ ማመስገን በዓለ መላእክት የተለመደ ነው፡፡የመላእክት እህት የሆነች እመቤታችንም ከነፍሷ የሆነ ምስጋናዋን በዚሁ ሰማያዊ በሆነ ምስጋና ገልጻለች፡፡ ይህም ከመላእክት ጋር የነበራትን የምስጋና ኅብረት ያሳያል፡፡ከዚህም በግላችንም ሆነ ለፍጥረተ ዓለም ለተደረገው የእግዚአብሔር የቸርነቱ ሥራ ማመስገን የተገባ መሆኑን ለሁላችን ትምህርት ትታልናለች፡፡

እመቤታችን ፈጣሪዋናአምላኳ እንዲሁም ልጇ የሆነውን እርሱን ማመስገን ብቻ ሳይሆን፤በእርሷ ላይ በተደረገው ድንቅ ነገር ትውልድ ሁሉ ሲያመሰግኗት ሲያደንቋ እንደሚኖሩም ገልጻለች፡፡በዚህም የተነሳ እውነተኛዋ የሐዋርያ ቤተክርስቲን ልዑል እግዚአብሔርን ከማመስገን ለጥቃ  እመቤታችንን በውዳሴ በቅዳሴ በማንሳት ታመሰግናለች፡፡ ልጆቿም በነገር ሁሉ በንጽሕናና በቅድስና በማጌጥ እናታቸውን ቅድስት ድንግል ማርያምን እንዲመስሉ ታስተምራለች፡፡ ቤተክርስቲያን በማኅሌቱ በቅዳሴው በሰዐታቱ በስብከቱና በትምህርቱ ሁሉ ደጋግማ እመቤታችንን የማንሳቷ ምስጢር በንጽሕናና በቅድስናዋ አብነት በመሆን በአማላጅነቷም ፍጹምነት ወደ እግዚአብሄር እቅፍ የምታደርሰን በመሆኗ ነው፡፡

ከጥንት ሲወርድ ሲወራረድ የመጣው ትክክለኛ ዶግማ ኖናና ትውፊት እንዳይበረዝ እዳይከለስ በማስተማር ጠብቃ ማቆየቷ የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያንን ከማንም በላይ ሐዋርያት ከጌታችን የተቀበሉት የጥንታዊውና የእውነተኛው ክርስትና የታመነችባለ አደራ ቤተ መዘክር ያደርጋታል፡፡

ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር!

                                               እንኳን ለጾመ ፍልሰታ ለማርያም በሰላም አደረሰን!

                                                                 ቀሲስ ታምራት ውቤ

ነሐሴ 2007 ዓ.ም

Read more...

ጠቃሚ አድራሻዎች

መጻሕፍት ቢያነቧቸው

  • * ​ፍቅር 
  • ፍና ቅዱሳን
  • * የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ሕይወቱ እና ትምህርቱ 
  • * ዝጎራ